Sunday, May 6, 2012

ምሥጢረኛው ባለቅኔ - የጸጋዬ ገብረ መድኅን ‹‹አዋሽ››




ባለቅኔውና ጸሐፌ ተውኔቱ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን (1928-1998) በኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍ ታሪክ ውስጥ ሁነኛ ስፍራ አላቸው፡፡ በአማርኛና በእንግሊዝኛ በጻፏቸው ልጨኛ (ማስተርፒስ) ሥራዎቻቸውም ግኑን ናቸው፡፡
ከአምስት ዓመት በፊት የካቲት 18 ቀን 1998 ዓ.ም. ያረፉት ሎሬት ጸጋዬ ከጻፏቸው መጻሕፍት አንዱ ‹‹እሳት ወይ አበባ›› የሥነ ግጥም መድበል ነው፡፡

‹‹ምሥጢረኛው ባለ ቅኔ›› የተሰኘ በደራሲው ጥበባዊ ሕይወት ዙሪያ መጽሐፍ ያሳተሙት አቶ ሚካኤል ሺፈራው፣ በቅርቡ ‹‹አንድምታ ወሐተታ ዘጸጋዬ ገብረ መድኅን›› በሚል ርእስ በአንድ መድረክ ላይ ጥናታዊ ጽሑፍ አቅርበው ነበር፡፡

በ‹‹እሳት ወይ አበባ›› መድበል ላይ ባተኮረው ጥናት ከቀረቡት ሐተታዎች መካከል ‹‹አዋሽ›› በተሰኘው ሥነ ግጥማቸው ዙርያ የሰጡትን አንድምታ እንዲህ አቅርበነዋል፡፡

*********
ጸጋዬ ገብረ መድኅን በመጨረሻው ዘመኑ የራሱን ሥነ ግጥሞች ባነበበት ሲዲ ላይ ስለ አዋሽ ሥነ ግጥም ምሳሌያዊነት ሲናገር በሌሎችም አገሮች የየአገሩ ባለቅኔዎች ታላላቅ ወንዞቻቸውን በአገራዊ ምሳሌአዊነት እንደሚወክሏቸው ያነሣል፡፡ ታላቁ ቴብስ በእንግሊዝ፣ ሚሲሲፒ በአሜሪካ፣ ቮልጋ ወይም ዶን በሩሲያ፣ በአገራዊ ምሳሌያዊነታቸው የየአገሩን ታሪክና ባህል ሲወክሉ መኖራቸውን ይናገራል፡፡

በ‹‹ምሥጢረኛው ባለቅኔ›› መጽሐፌ የአዋሽን ምሳሌያዊነት በሁለት መልክ ለማሳየት ሞክሬ ነበር፡፡ አንደኛው ባለቅኔው ራሱ እንዳለው ባገራዊ ምሳሌያዊነቱ ነው፡፡ ሁለተኛውና ባለቅኔው ያላለው ደግሞ አዋሽ የባለቅኔው የገዛ ሕይወቱ ምሳሌያዊ ውክልና መሆኑን ነው፡፡ አገራዊ ምሳሌያዊነቱን በሁለተኛ ደረጃ ለማስረዳት እስቲ በመጀመርያ አዋሽ የጸጋዬን ሕይወት በምን መልክ እንደወከለ ለማሳየት ልሞክር፡፡

በእኔ ንባብ አዋሽ ሥነ ግጥም ላዩን ወይም ሰሙን ብቻ ላነበበ ስለወንዙ የተጻፈ መወድስ ሊመስለው ይችላል፡፡ ሥነ ግጥሙ ባለሦስት ንጣፍ የቅኔ አነባበሮ መሆኑን እምንረዳው ወርቅና ምናልባትም አልማዙ ሲገለጡልን ነው፡፡ ከእዚህ ላይ ወርቁ ወይም ሁለተኛው ንጣፍ የግጥሙ አገራዊ ውክልና ነው፡፡

በዚህ ሥነ ግጥም አዋሽ በአገራችን ባህልና የታሪክ ጉዞ ተመስሏል፡፡ በለጋስነቱ በባለጸግነቱ ያገርን ዙርያ ጥምጥም ሁሉ በማዳረሱ ስልም በንፉግነቱ በአገራችን የታሪክ ጉዞ ተመስሏል፡፡ ዘለዓለም በማያቋርጥ ጉዞው በስተመጨረሻው አረህ አለምልሞ በረሃ ላንቃ በመዋጡ ፍሬ ሊያፈራ ባለመቻሉ በታላቅ ሐዘን ባገራችን የታሪክ ጉዞ ተመስሏል፡፡ በሌላም በኩል በተስፈኝነቱ ወደ ምሥራቅ በመፍሰሱ በታሪክ በረሃ ውስጥ ከዘለዓለም እስከዘለዓለም ሲፈስ ጨርሶ በማይሞተውና በማይደመሰሰው በተስፈኛ መንፈሳችን ተመስሏል፡፡

‹‹እስከ መቼ ይሆን አዋሽ ......... አዋሽ በቃኝ አትል ቆራጥ፣
ማን ያስተማረህ ፈሊጥ ነው አረህ ለማለምለም መዋጥ፣
አሻቅበህ ወደ ምሥራቅ ወደ ጀምበር መውጫ መናጥ፣
ሰምጠህ ልትቀር በሐሩር ማጥ፣››
የሐበሻ ታሪክ ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም የተዘረጋው የሐበሻ ታሪክና ባህል በተለይም ደግሞ ጸጋዬ ባለፈበት ዘመን በዚያ ሁሉ የዘመን ጉዞ በመጨረሻ ሽሚያና ቅሚያ የነገሠበት እንደጸጋዬ አገላለጽ ፍግ የሚለመልምበት ፍቅር የሞተበትን ትውልድ በማፍራት/ በማለምለሙ ሲያዝን አዋሽን በአገራችን ጉዞ ተወክሎ እናየዋለን፡፡

ይሁን እንጂ ይህ ምሳሌ የጸጋዬ ሥነ ጥበባዊ ሕይወት ምሳሌም ጭምር ነው፡፡ ይህ ደግሞ ሦስተኛው ንጣፍ መሆኑ ነው፡፡

ሁሉም እንደሚያውቀው ጸጋዬ ትውልድ ቀዬው ከመጫ ጊንጪ በስተደቡብ ሲል ቦዳ አቦ ነው፡፡ የአዋሽ ወንዝም መነሻ ከዚያው ከጊንጪ አላባ ጣፋ ተራራ ግርጌ ነው፡፡ የጸጋዬ የሥነ ጥበብ መንፈስና ሕይወት አገር ምድሩን ሁሉ ዙሮ በመጨረሻ በንፉግ ባህል በረሃ ተውጦ እንዲቀር አዋሽም አገር ምድሩን አካልሎ ከአሳይታ ማዶ አፋምቦ ተራራ ግርጌ አሸዋ ውስጥ ሰምጦ ይቀራል፡፡

‹‹መጫ ቋጥሮ ሸዋ ጸንሶ ሰባት ቤት ጉራጌ አርግዞ፣
ከዳዳ ምንጭ አሩሲ እምብርት ከነቅሪቱ ተጉዞ፣
ከአላባ ጣፋ ሼህ ሁሴን አዳል ሞቲ ሽሉን ይዞ፣
ከከረዩ ማታ ሓራ ከኢቱ እስከ አፋር አምጦ፣
አሸዋ ነክሶ ቀረ አዋሽ ከነጽንሱ አረህ ሰምጦ፣
በምድረ በዳ ጉረሮ በረሃ ላንቃ ተውጦ፤›› ይለናል፡፡ በዚህ የአዋሽ የአገር ዙር ጥምጥም ጉዞና ፍጻሜ ውስጥ ጸጋዬ የራሱን ምስል ሥሎልናል፡፡ እርሱ በሥነ ጥበቡ ዘልቆ ያልገባበት የአገርና የባህል እልፍኝ የለም፡፡ በእሳት ወይ አበባ ሥነ ግጥም መድበል እንኳ ከዓባይ ኑቢያ ዘመን ሥልጣኔ አንሥቶ የኦሮሞን ጋዳ ሥርዓት፣ ባህልና ለዛ በ‹‹አቴቴ ዱብራ ኦሮሞ››፣ የኦሮሞን ጀግና መንፈስ ‹‹በቦረን የሃዩ አላኬ ሊበን ቀረርቶ››፣ በ‹‹አንኮበር›› የአመሃየስ በር የቤተ አምሃራን ፖለቲካና ባህል፣ ወደ ውስጥ ዘልቆ፣ የሩቁን አቅርቦ ከታሪክና ከባህላችን ሊያስተዋውቀን ሲቃትት እናደምጠዋለን፡፡ ከታሪክ ምዕራፎቻችን ዓድዋና ማይጨው፣ መተማና ዶጋሊን፣ በምናቡ አቅርቦ በዘለለት ሩጫ ዝንጋኤ ማንነቱ ለጠፋበት ትውልድ የማን ልጅነቱን ሊያስታውስ ሲጥር እንሰማዋለን፡፡ ከዘመን ጀግኖቻችንን ረስተን ማንነታችን እንዳይሰወርብን ቴዎድሮስን፣ ጴጥሮስን፣ ዮሐንስን፣ ከሞት አስነሥቶ ሁለተኛ ልደት ሲሰጣቸው በመድረክም በሥነ ግጥምም ስንመለከት ኖረናል፡፡ በጥሞና ዘልቀን ካስተዋልናቸው እኒህና ሌሎቹ ሁሉ ጥልቀታቸውና ለኛ ትውልድ ሕይወት ያላቸው ፋይዳ ታላቅ ነው፡፡ እናም ጸጋዬ ይህን በመሰለው የሥነ ጥበብ ሕይወቱ ነው አገር ምድርን በሚያካልለው በአዋሽ የተመሰለው፡፡ ጸጋዬ የሥነ ጥበባዊ ሥነ ልቡናውን የጸነሰው ከትውልድ መንደሩ ከአምቦ ነው፡፡ ከመጫ፡፡ አፈጻጸሙም ‹‹በንፉግ ባህል ውስብስብ ጫካ በቁም እያለ መረሳት፣ አሊያም ቢታወስም ለቁም ነገሩ ዋጋ የማይሰጥ ውዳሴ ከንቱ መሞካሸት በቀር፣ የዘራውን ሳይቅም የወለደውን ሳይስም በከንቱ የመቅረቱ ምሳሌ ነው፡፡››

‹‹መጫ ቋጥሮ ሸዋ ጸንሶ ሰባት ቤት ጉራጌ አርግዞ
ከዳዳ ምንጭ አሩሲ እምብርት ከነቅሪቱ ተጉዞ
ከአላባ ጣፋ ሼህ ሁሴን አዳል ሞቲ ሽሉን ይዞ
ከከረዩ ማታ ሓራ ከኢቱ እስከ አፋር አምጦ
አሸዋ ነክሶ ቀረ አዋሽ ከነጽንሱ አረህ ሰምጦ፡፡››
ይህም የተሣለልን በዕድሜ ልክ ጉዞ በአዋሽ ጉዞ ተመስሎ ነው፡፡ ወደ አፋር በረሃ ዘልቆ የአዋሽን ጉዞ ላስተዋለ ያን ሁሉ ዘመን ሲያለመልም የኖረውን አረህና አሜኬላ በሐዘን ይታዘባል፡፡ የጸጋዬም ረዥም የሥነ ጥበብ ሕይወት በታሪክ ብያኔ ሰበብ እምነትና ፍቅሩ የነጠፈ፣ ይልቁንም ለመጪው ትውልድ እሚያወርሰው ‹‹የሰብእና ብርሃን›› የሌለው ትውልድ ሲፈጠር በማስተዋሉ በምስጢር ከራሱ የተዋቀሰበት ሥነ ግጥም መሆኑን እናስተውላለን፡፡

‹‹እስከ መቼ ይሆን አዋሽ ..... አዋሽ በቃኝ አትል ቆራጥ
ማን ያስተማረህ ፈሊጥ ነው አረህ ለማለምለም መዋጥ
አሻቅበህ ወደ ምሥራቅ ወደ ጀምበር መውጫ መናጥ
ሰምጠህ ልትቀር በሐሩር ማጥ፡፡››
ይህን አረህ የማለምለም ርግማን በአዋሽ ብቻ ሳይሆን በቴዎድሮስ ምሳሌ በሣለው የራስ ምስልም ውስጥ እናገኘዋለን፡፡
‹‹ታዲያ እንግዲህ አንቺ ኢትዮጵያ እኛስ ልጆችሽ ምንድነን
አመንኩሽ ማለት እማንችል ፍቅራችን እሚያስነውረን
ዕዳችን የሚያስፎክረን
ቅንነት የሚያሳፍረን ቂማችን የሚያስደስተን
ኧረ ምንድነን? ምንድነን?››
አሜኬላ እሚያብብን
ፍግ እሚለመልምብን
ከአረም ጋር ያፈራን ጊንጦች ከእንክርዳድ ያልተለየን ዘር
ግርዱ ከምርቱ ተማጥቆ ከቶ ያልተበራየን መከር....››
በአዋሽ ሥነ ግጥም የተሣለው የጸጋዬ ውስጣዊ የኪሳራ ስሜትና ትካዜ ተስፋ ላለመቁረጥ የተደረገ ውሳጣዊ ሙግት ነው፡፡ ይሁንና ይኸው ውሳጣዊ ትግል ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርኩት የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊነት የታሪካችን ጉዞ ምስልም ነው፡፡

                                                   እሳት ወይ አበባ


እሳት ወይ አበባ

 ሌት ከዋክብቱ  እንደ ፀደይ
አጥለቅልቆን  በቀይ አደይ
ሰማዩ  ሥጋጃ  አጥልቆ
ተሽለምልሞ  አንጸባርቆ
ፈክቶ አሸብርቆ  ደምቆ
በአዝመራ  በአጥቢያ  ዐፀድ  ሰፍኖ
የዓደይ  አዝርዕት  ተከሽኖ
በዕንቁጣጣሽ  ሰብል  ታጥኖ
ኢዮሃ  አበባዬ  ሆኖ፥
ጨረቃዋ  ከቆባዋ፥  ከሽልምልሚት  እምቡጧ
ብላ ከሰንኮፈንዋ፥ ተንዠርግጎ የእንኮይ ቡጧ፥
ድንግል  ጽጌ-ረዳ  ፈልቃ
ፍልቅልቂት  ድምቡል ቦቃ
ተንሠራፍታ  የአበባ  ጮርቃ፥
ታድያን  ብሌኑ  የጠጠረ
ባሕረ-ሃሳቡ የከረረ
የውበት ዓይኑ የታወረ
ልበ-ሕሊናው  የሰለለ
አይ፥ አበባ አይደለም አለ፤
አይ፥ እሳት አይደለም አለ፤
ያልታደለ።
ሰማይ  ጨለማ  ነው እንጂ፥  እሳት አደል ብሎ ካደ
እቶን  ባይኑ  እየነደደ።
ከዋክብቱ  እንደ  ችቦ
በነበልባል  ወርቀ  ዘቦ
ከፅንፍ  ፅንፍ  አውለብልቦ
ደመራው  እየተመመ
እየፋመ  እየጋመ
ደመና  እንደንዳድ  ሲነድ
መንጸባርቅ  ሰደድ  ሲወርድ፥
በራሪ  ኮከብ  ተኩሶ
በአድማሳት  እሳት  ለኩሶ
ይኸ እንደኔና  እንዳንቺው፥  የውበት ዓይኑ  የሰለለ
ሰማይ ጨለማ ነው እንጂ፥  እሳት እኮ አይደለም አለ፥
ያልታደለ።

ይቅር ብቻ  አንናገርም፥
እኔና  አንቺ  አንወያይም፤
ለውይይት  አልታደልንም
እንዲያው ዝም፥ እንዲያው ዝምዝም።
አበባ አንሆን ወይ እሳት
ተጠምደን  በምኞት  ቅጣት
ሰመመን  ባጫረው  መዓት
ዕድሜ አችንን እንዳማጥናት፤

እሳት አንሆን ወይ አበባ
በሕቅ  እንቅ  ስንባባ
ባከነች  ልጅነታችን፥ እየቃተትን ስናነባ
ሳንፈጠር  በሞትንባት
ሳናብብ  በረገፍንባት
ሳንጠና ባረጀንባት
አበባ ወይንም እሳት፥  መሆኑን ብቻ አጣንባት።

Friday, May 4, 2012

በውቀቱ ስዩም

www.facebook.com/tarikuasefaክልክል ነው

ማጨስ ክልክል ነው
ማፍዋጨት ክልክል ነው
መሽናት ክልክል ነው
ግድግዳው በሙሉ ተሰርቶ በክልክል
የቱ ነው ትክክል?
ትንሽ ግድግዳና ትንሽ ኃይል ባደለኝ
"መከልከል ክልክል ነው"፤ የሚል ትዕዛዝ አለኝ፡፡


(በእውቀቱ ስዩም፣ የ፣ሣት ዳር ሐሳቦች፣ 2000)
 ደመወዙን ቢጥል
አንስተው ጠጡበት
ባርኔጣውን ቢጥል
ወስደው ደመቁበት
ከዘራውን ቢጥል
ተመረኮዙበት
በሄደበት ሁሉ
እየተከተሉ
በጣለው ሲያጌጡ
በጣለው ሲያተርፉ
ራሱን ሲጥል ግን
አይተውት አለፉ

በውቀቱ ስዩም
(ካንድምታ ላይ የተወሰደ )
 መሆን አለመሆን

በመሆን እና ባለመሆን
በማድረግ እና ባለማድረግ
በሁለት ታዛዦች ስር መውደቅ ነው
ሰው የመሆን ትልቅ ህግ
ሊኖሩት በማይፈቅዱት ህግ
ሊፈጽሙት በማይሹት ስህተት
በጣምራ ግጭቶች መሃል መቆም ነው ሰው የመሆን ሰውነት
ይሄ ሁሉ ፍጡር ይሄ ሁሉ ፍጡር
በፍጥረት መድረክ ላይ የሚርመሰመሰው
ላንዲት ቅጽበት እንካን ሰው ሆኖ አያውቅም ሰው ሊሆን ጽንስ ነው
ሰው እስኪሆን ድረስ አንዳንድዜ አምላክ አንዳንዴ ሰይጣን ነው።
ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
መሸ ደግሞ አምባ ልውጣ!

አምባ ወጥቼ እኩለ-ሌት ፤ ስለት ገብቼ በስሟ
ከርሞ ሰይጣን በሷ አስቶኝ፤ ልገላገል ከህመሟ
ጠበሏ አፋፍ በጨረቃ፤ ደጋግሜ፤ ማህሌት ቆሜ
ሆዴ ቃትቶ ባር ባር ብሎ፤እርቃኔን ከሷ ታድሜ
ደጀ ሰላሟን በአራት እግር፤ ተንበርክኬ ተሳልሜ
በስጋዬ እሚነደውን፤ በጸሎት ላቤ አጣጥሜ
እፎይ ብዬ አመስግኜ፤ ውዳሴዋን ደጋግሜ...
ገና ከደጅዋ እልፍ ሳልል፤ ደሞ ይምጣ የቁም ህልሜ?
ሌት በጥምቀቷ የነጣው፤ ነጋ፤ ደፈረሰ ደሜ።
ለሷ እንጂ ለኔ አልያዘልኝ፤ አዬ የስለት አታምጣ!
በውጣ ውረድ በጠበል፤ ባሣር ወዜ ቢገረጣ
ልክፍቷ እንደሁ አልለቀቀኝ፤ መሸ ደሞ አምባ ልውጣ!

ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድሀን፣ እሳት ወይ አበባ

Thursday, May 3, 2012

ይድረስ ለእናት አለም


ይድረስ ለእናት አለም፡-www.facebook.com/tarikuasefa

በጣም ለምወድሽ እናቴ እናት አለም ! እንደምን ሰንብተሻል

አባበዬስ እንዴት ነው? እኛ ከወንድም ጋሼ ፀባይ መለዋወጥ

በስተቀር ደህና ነን፡፡ እናት ዓለም ብቻ አንድ ወንድ ልጅሽን ያቺ

ቀልቃላ ገርል ፍሬንዱ ምን እንዳስነካችው ባይታወቅም አብሮን

እንዳልተወለደ አሁንማ ስልኩንም ለማንሳት ኮርቷል፡፡

በየሳምንቱ እሷን ይዞ በየሀገሩ መብረር አምጥቷል፡፡

እናት አለም! እናንተ ለፍታችሁ አንዴ ፈረንሳይ ት/ቤት፤

አንዴ ፈረንጅ ሀገር ብር እየመነዘራቸሁ አስተምራቸሁ ዛሬ

ይቺ ከይሲ በአናት መጥታ የተዘጋጀ እና ያማረ ቤት ልትገባ

ዳር ዳር ትላለች፡፡ በዛ ላይ ደግሞ እሱ እሷን ተዋወኩ ብሎ

አዲሰ ማርቼድስ አውጥቶ የድሮውን ቢ..ኤም..ደብሊው ለእኔ

ይሰጠኛል ስል እሷው በቀደም ይዛው ስትደናብር መሀል ከተማ

Aየኋት፡፡ በዛ ላይ አለባበሷን ብታይ እኮ ጭንቅላትሽን ይዘሽ

ትጮሂያለሽ፡፡ የተወለደ ሀጻን ጭንቅላት የሚያካክሉትን

ጡቶቿን እያሳየች ነው የምትሄደው፡፡ ትንሽ እንኳን እፍረት

የሌላት ጉድ በየድግሱ ቤት ወንበር እያለ እሱ ላይ ነው

የምትቀመጠው፡፡ ሌላው ደግሞ እንደ በሽተኛ እሱ ነው

የሚያጎርሳት ብትሞት በእጇ አትበላም፡፡ እኔማ ገና ሳያት ነው

ደሜ የሚፈላው፡፡

ብቻ ልጅሽን ምን እንዳስነካችው እራስሽ መጥተሽ

ብትጠይቂው ይሻላል፡፡ በዚያን ሰሞን ቹቹ የመኪናዋ ቁልፍ

ጠፍቶ ስራ ውሰዳት ብዬ ብደውልለት ታከሲ ይዛ ትሂድ ስብሰባ

አለበኝ አለኝ፡፡ ለድሮው የእኛ ነገር የማይሆንለት ይኸው እሷን

ካገኘ ወንድምነቱን ሁሉ ረስቶታል፡፡ ከሁሉ ከሁሉ የምፈራው

አውቃ አርግዛበት ጠቅልላ ለመግባት ሠርጌን ደግስ እንዳትለው

ነው፡፡

እንደው አናት አለም እሷን ካገኘ ፀባዩ ሁሉ ተቀያይሯል፡፡

ባለፈውማ ይባስ ብሎ ለልደቱ የገዛሁለትን የሱን ቱታ ለብሳ

ስፖርት ስትሰራ ስፖርት ቤት አገኘኋት፡፡ ደግሞ አማረብኝ ብላ

ያንን እሱው ያሰራላትን ነጭ ጥርሶቿን ታሳየኛለች፡፡

እንደማትወደኝ እኮ ያስታውቅባታል!! ከሁሉ ከሁሉ ቹቹ ታክሲ

ይዛ ትሂድ ያለውን አልረሳውም፡፡ እናት አለም መቼም ጉድሽን

የሚነገርሽ የለም ብዬ ነው የምጽፍልሽና ነገ ጠዋት አንቺንም

በዚች በቀዥቃዣ ሳይለውጥሽ አንድ ነገር አድርጊ፤ ምንም

ቢሆን እኛ ሥጋዎቹ ነን፤ ከአንድ ሆድ የወጣነውና አንድ ጡት

ጥበተን ያደግነው እኛ ነን፡፡ እሷ ባዳ ናትና አንድ ነገር አድርጊ፡፡



                                                      ልጅሽ ሳሮን

የእናት አለም የመልስ ደብዳቤ

ለምወድሽ ልጄ ሳሮንዬ ለመሆኑ የላከሺልኝን ደብዳቤ ሰትጽፊልኝ ምን

ዓይነቱ ስይጣን ነው ሰፍሮበሽ የነበረው! እንዲህ ዓይነት ልጅ ነው

የወለድኩት አሰኘኝ፡፡ እግዚአብሔር የቀንና የማታ ጸሎቴን ሰምቶ ለአንድ

ወንድ ልጄ ውሃ አጣጭ የትዳር ጓደኛ ቢሰጠው የአንቺ እንቅልፍ ማጣት

ምን ይባላል?

የእኔ ልጅ! እንዳልሽው ከአንድ ሆድ የወጣችሁ አንድ ጡት ጠብታችሁ

ያደጋችሁ ወንድምሽ ነው፡፡ ወንድም እህቱን እንዲያገባ ሃይማኖታችንም

ባህላችንም አይፈቅድም፡፡ ወንድምሽን አንቺ አታገቢው፤ ምን አድርጊ ነው

የምትያት? የእኔ ልጅ ይኼው እሷን ካገኘ ጊዜ ጀምሮ የላከልኝ ፎቶ

ይኸው መልኩም መለስ ብሏል፡፡ በሳምንት በሳምንትም ይደውልልኛል፡፡

እሷንም በስልክ ደውሎ አስተዋውቀኝ፡፡ አደራ ብያትም ይኼው የሆቴል

ምግብ ከበላ ሰንበቷል፡፡ የልጄን ደስታ በድምፁ አውቀዋለሁ፡፡ ይኼው

እናንተ ስትለመኑ ሰው እየፈለግን ነው ያላችሁትን መድኀኒት እንኳን

እሷም አይደለች እንዴ የፊት ቅባት ሳይቀር ጨምራ በፖስታ ቤት

የላከችልኝ፡፡ ሌላው ደግሞ ነርስ ነች አለኝ፡፡ ልጄ ቢያመው እንኳን አጠገቡ

አለችለት፡፡

አንዳታረግዝ ነው የምፈራው አልሺኝ? በየቤተክርስቲያኑ የምሳለው ስለቴ

ደርሶልኝ የሱን ፍሬ ሳልሞት ባይ ምናለበት፡፡ አንድ ሳይሆን መንታ መንታውን

ባረገዘችልኝ፡፡ አንቺ የሰው ኑሮ ውስጥ ገብተሸ ከምትበጠብጪ ሰው መናቁን

ትተሸ ብታገቢ ለወሬም ጊዜ አየኖርሽም ነበር፡፡

የእኔ ልጅ! ጡቷን ማሳየት ቀርቶ ራቁቷን ብተሄድ ፖሊስ ካልያዛትና ልጄ

ከወደዳት አንቺ ምን ጥልቅ አደረገሽ? ቢወዳትም አይደል እንዴ እዚህ ድረስ

ደውሎ ያስተዋወቀኝ፡፡ የኔ ልጅ መፅሀፉም የሰው ልጅ እናት እባቱን ይተዋል፤

ከሚሰቱ ወይ ከባሉ ጋር እንድ ይሆናል ነው እንጂ የሚለው ወንድም እህቱን

ያገባል አይልምና ወደ መንፈስሽ ተመልሰሽ አምላክሽን ይቅርታ ጠይቂ፡፡

የወንድምነቱን ከሚገባው በላይ አድርጓል ወይስ እድሜ ዘላለሙን እናንተን

ሲያስተምርና መኪና ሲገዛ እንዲኖር ነው ምኞትሽ፡፡

ልጄ! ልብ ብለሽ አያትሽ የነገረኝን ይሄንን አፈ ታሪክ አንበቢ፡፡

“ሚስት ከባልዋ ተጣልታ ዛሬውኑ መጥታችሁ ካላፋታቸሁኝ ራሴን

እገላለሁ ብላ አናት አባቷ ጋ መልእከተኛ ትልካለች፡፡ እናትና አባትም

ደንግጠው ሊያፋቱ ሲከንፉ በሌሊት ልጃቸው ቤት ይሄዳሉ፡፡ ድንገት በሩን

ከፍተው ሲገቡ ልጃቸው ከአልጋዋ ዘላ ወርዳ ራቁቷን ትቆማለች፡፡

ድንገትም በር የከፈቱት እናትና አባቷ መሆኑን ስታይ አፍራ ቶሎ ብላ

ፊቷን ወደ ባሏ ጀርባዋን ደግሞ ወደ እናትና አባቷ አዞረች፡፡ ምንም

እንኳን ልትፈታው የተዘጋጀችው ባሏ ቢሆንም ባሏን ሳታፍር እናትና

አባቷን አፈረች፡፡”

ልጄ ሳሮን የእናትና የአባት ፍቅር ዘላለማዊ ቢሆንም የወላጅንም ውለታ

መመለስ ተገቢ ቢሆንም ከባልና ከሚስት የቀረበ የለም፡፡ ስለዚህም ነው

ባልና ሚስት አንድ አካል አንድ አምሳል ናቸው የሚባለውና ቦታሽን

Aውቀሽ የሰውን ሕይወት አትበጥብጪ፡፡ አፍ አለኝ ብለሽም እንዲህ

አይነት አሉባልታ ሁለተኛ እንዳትጽፊልኝ፡፡ አንቺ አግብተሸ ብትወልጂ

ወንድምሽ ደስ እንደሚለው ሁሉ ለእሱም አንቺ ደስ የበልሽ፡፡

እግዚአብሔር ጥሩ ልቦና እንዲሰጥሽ እጸልይልሻለሁ፡፡

እናትሽ እናት እለም

Thursday, April 19, 2012

አምስቱ ዓይነት ኢቫንጋዲ - የሐመሮች ትውፊት

www.facebook.com/tarikuasefa

(በምዕራፍ ብርሃኔ)

ኢቫንጋዲ ሐመሮች ለዘመናት ያቆዩት ባህላዊ ጭፈራቸው ነው፡፡ በቅርስ ጥናትና ባለሥልጣን በታተመ አንድ የኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርሶች ኢንቬንቶሪ እንደጠቆመው፣ ‹‹ኢባን ማለት ምሽት ማለት ሲሆን፣ ጋዲ ማለት ጭፈራ ወይም ዝላይ ማለት ነው፡፡››
ጭፈራውን የሚያደርጉት ወጣት ሴቶችና ወንዶች ሲሆኑ፣ ጭፈራው ሲጋመስ በእድሜ የገፉ ወንድና ሴቶች ለክብራቸው ተለምነው እንዲጨፍሩ ይደረጋል፡፡

ኢቫንጋዲ በአምስት ምክንያቶች ይጨፈራል፡፡ የመጀመሪያው ምክንያት እህል ሲሰበሰብ የደስታና የፌሽታ ጊዜ ስለሚሆን ሁሉም ተሰባስቦ ጭፈራው ይካሄዳል፡፡ በተቃራኒው ደግሞ ረሃብ ሲሆን ችግራቸውን፣ ድካማቸውንና ረሀባቸውን እንዳያስቡ ሲሉ በጭፈራው ሰውነታቸው አድክመው ለመተኛነት ይጠቀሙበታል፡፡ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ አርብቶ አደሩ ለመፎከሪያነት፣ ለማሞገሻነት የሚጠቀምበትን ቁመናውም ሆነ የቀንድ አበቃቀሉ ልዩ የሆነውን ሰንጋ በሬ እድሜው ሲገፋ፣ ጓደኞቹ እንበላለን ሲሉ ኢቫንጋዲ ይጨፈራል፡፡ ‹‹ይህ ኬንያ ጠረፍ ድረስ ወስጄ ግጦሽ አስግጬዋለሁና ጀግና በሬዬ ነው፤›› በማለት ኩራቱን የሚገልጸው አርብቶ አደር ብዙ ጥይት ተተኩሶ በሬው ሲታረድበት እሱ ሲያለቅስ፣ ጓደኞቹ ደግሞ በደስታ በመፍለቅለቅ ይበሉታል፡፡ ሦስተኛው ምክንያት ደግሞ ልጃገረዶች እየጨፈሩ ወደ ሰው ቤት በመሄድ እህል ይሰበስባሉ፡፡ ወንዶች ደግሞ ቅቤ ገዝተው ያመጣሉ፡፡ ከዛ ሴቶቹ ምግቡንና መጠጡን ካስተካከሉ በኋላ ማኅበረሰቡ ተሰብስቦ ኢቫንጋዲ ይጨፍራል፡፡ አራተኛው የኢቫንጋዲ ጭፈራ የሚካሄደው ደግሞ አንድ ወንድ ሊያገባ ሲል ከስምንት እስከ አሥር የሚሆኑ ሰንጋ በሬዎች ጭራቸውና ቀንዳቸው ባላጩ ነገር ግን ለማጨት እየተዘጋጁ ባሉ ወንዶች ተወጥሮ በበሬዎቹ ጀርባ ላይ እየተረማመደ ይዘላል፡፡ ሙሽራው (እኩሌ) ዓይነ ስውር ወይም አካል ጉዳተኛ ከሆነ ከብቶች ተደርድረው በአንገታቸው ስር እንዲሾልክ ይደረግና ዘሏል ይባልለታል፡፡ እኩሌው ይህን በፈጸመ ማግሥት የኢቫንጋዲ ጭፈራ ይደረጋል፡፡

አምስተኛው ዓይነት ደግሞ ነዋሪዎቹ በጎብኚዎች ጥያቄ ኢቫንጋዲን የሚጨፍሩበት ነው፡፡ ከሚጨፍሩበት ባህላዊ ዐውድ ውጪ በመጫወታቸው፤ ክፍያ ይጠይቁበታል፡፡

የኢቫንጋዲ ጭፈራ ሲካሄድ በአካባቢው ስላለው ችግር፣ ስለጠፋ በሬ፣ ጥሩ የሳር ግጦሽና ውሃ የት እንዳለ የሚጠቋቁምበትና አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን የሚለዋወጡበት አጋጣሚ ነው፡፡

ኢቫንጋዲ ሲጨፈር ቦርዴ (ባህላዊ አልኮል መጠጥ) ይጠጣል፤ ከብት ይጣላል፤ ፍየል ይታረዳል፡፡ ሐመሮች የተጣለው ከብት ሆድ እቃ ሲዘረገፍ የሚወጣው ፈርስ ውስጣዊም ሆነ ውጫዊ አካል ላይ ያለባቸውን በሽታ ይፈውሳል ብለው ስለሚያምኑ፣ ከተሰበሰበው ሰው ውስጥ ታማሚ ነኝ ያለ የበሬውን ፈርስ ይጠጣል፤ ወይንም ደግሞ ገላውን ይቀባል፡፡ በወቅቱ የተጣለው በሬ ስጋ በእንጨት ውስጥ እንዲሾልክ ተደርጎ በክብ ይደረደርና በመሃል ላይ ትልቅ ግንድ በእሳት ተለኩሶ በወላፈኑ ይጠበሳል፡፡
የተጠበሰውን ስጋ የሚበላ እንዳለ ሁሉ ጥሬ ጨጓራን የሚበሉም አይታጡም፡፡ በኢቫንጋዲ ጊዜ ዘመድ፣ ወዳጅ፣ ጎረቤትና ጓደኛ ተሰባስቦ ማውጋቱ፣ መብላቱ መጠጣቱና መጨፈሩ እጅግ ያይላል፡፡

በኢቫንጋዲ ጭፈራ ላይ በሰፊው የሚሳተፉት ወጣቶች ቢሆኑም ሽማግሌዎችና አሮጊቶች ተለምነው ለተወሰኑ ደቂቃዎች ቢጨፍሩም መድረኩን ለወጣቶቹ መልሰው ያስረክባሉ፡፡ ሁሉም የቀረበለትን ቦርዴ ስለሚጠጣ የስካር መንፈስን በስሱ ያስተናግዳል፡፡

ጭፈራው ሲጀመር ወንዶቹና ሴቶቹ ፊት ለፊት ይደረደራሉ፡፡ ወንዶቹ እየዘፈኑ ዘለል ዘለል እያሉ በክብ ሲሽከረከሩ፣ ሴቶቹም ዘለል ዘለል እያሉ ወደ ወንዶቹ በመሄድ የሚፈልጉትን ጎረምሳ በእግራቸው መታ አድርገው ይዞራሉ፡፡ ወንዱም ስለተመረጠ ከሴቷ ኋላ ኋላ እየዘለለ ይጨፍራል፡፡ እርሷም ሰውነታቸው እንዳይነካካ በሚመስል ሁኔታ እየሸሸች እና እየተዟዟረች ትጨፍራለች፡፡ ጭፈራውን ልክ ሲያሳርጉት ወንዶቹ ወደ ቦታቸው ሲሄዱ ሴቶቹም በሩጫ ወደ ቦታቸው ይመለሳሉ፡፡ ሮጣ የሄደችውን ሴት ሲያስደንሳት የነበረው ወንድ ተከትሎ ከኋላዋ በመቆም ከወገቡ ወደፊት ለመጥ፣ ከጉልበቱ ደግሞ ሰበር ብሎ መቀመጫዋን ይነካታል፡፡ ከዚያም እርሷም ትሽኮረመማለች፤ እርሱም ወደ ቦታው ይመለሳል፡፡ እንዲህ እንዲያ እያለ ጭፈራው ይቀጥላል፡፡

አብረው የሚጨፍሩት ፍቅረኛሞች ወይም ደግሞ የሚከጃጀሉ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ በኢቫንጋዲ ላይ  ከተገናኙ ግን ከጭፈራው በኋላ ወሲብ መፈጸማቸው አይቀሬ ነው፡፡ ወሲብን ከትዳር በፊት መፈጸም ለሐመሮች ነውር አይደለም፡፡ ወንዱም ሆነ ሴቷ ለሌላ ሰው ለመዳር የታጩ እንኳን  ቢሆኑም ወሲብን ሲፈጽሙ እጅ ከፍንጅ አይያዙ እንጂ የሚከለክላቸው ምንም አይነት ሕግ የለም፡፡
www.facebook.com/tarikuasefa 

ጥቁር ሰው

The Teddy Afro Phenomenon: An Analysis

Published: Apr 17, 2012 by bini Filed under: Article Ethiopian News Views: 8,046 Tags: Teddy Afro, Tekur Sew, Des Yemil Sekay, Teddy Afro, Tikur Sew
Share663


Tewodros Kassahun aka Teddy Afro may not have a strikingly different and out of the ordinary voice. But he has a strikingly different manner, philosophy, view and poems. A “controversial” singer of the new breeds of intellectual Ethiopian artists, thinkers and philosophers, Teddy Afro has released his contentiously controversial album, Tekur Sew (Black Person). A short analysis follows.
Teddy Afro

A Book about Teddy Afro…

One of the very few musicians whose life story has been written is Teddy Afro in today’s Ethiopia.  A young writer who goes by the name Abel Zebene wrote a book titled “Ye Teddy Afro Talakent Mister” literally meaning the secrets of Teddy Afro’s greatness two years ago in 2010. The amateurishly written but well composed book does a secondary review of Teddy’s biography and assesses why the singer was so popular. The book calls Teddy a “revolutionary singer”. According to Abel, it was since Teddy Afro started singing that art received its due place within the society and music albums started to be sold as much as millions of birr.  The writer also states that Teddy regards freedom as his highest virtue in life and fears nothing but God. Ye Teddy Afro Talakent Mister also states that Teddy Afro loves his dad so much. His late father, Kassahun Germamo was a popular journalist and MC. His father is said to be behind the nurturing of today's ethical, nationalist, unitary, loving and wise Teddy. Teddy had one big difference with his dad...Music...his Kassahun wanted the young Teddy to be a Medical Doctor. Teddy loved music. However, Teddy was a high ranking student. Until he completed his matriculation, the author says, Teddy competed with the best ranking students and was his friends were the studious students.

Singing about three major themes; humanity, unity and love

A critical element that is lacklustre within the Ethiopian musicography is capability of researching, analysing, writing meaningfully, emotive-expressive issue based lyrics and arranging music. Up until recently, almost all singers had written no poems,  composed no song, they only joined art because they had “good” voice. They all were signing/yelling machines proffered lyrics, melody and arrangements by others. They were simply conduits. This resulted in the absence of creativity and originality in music. Almost all songs were about love and hate of a girl friend and boyfriend. Radically though, the happening of Teddy Afro converted that. Music became a timely, emotive, expressive and philosophically researched output. The major make-ups that make Teddy stand out as a popular music player are his unwavering and icebreaking thoughts and philosophies. Teddy is one of the few musicians to cover, sing and preach about justice, ''unity'' and political reconciliation between Ethiopia and Eritrea.  He sings about the unity of Ethiopians. The godly nature and eminence of love is also preached by the young man. He listens to the cries and problems of the public and echoes it. He sermonizes that we should have our own heroes and recognise them: Haile Gebresellaise, Kenenisa Bekele, HIM Emperor Hailsellasie and now King Menelik and his war comrades are some of them. The issue of street children, poverty, HIV/AIDS, lack of political/administrative progress or change, freedom and justice are some of his topics that he often raises and advocates.

In the civil rights movement of the United States and in the road to Zimbabwe’s independence, music played an essential role of unifying the freedom fighters and the masses at the same time raising their morale through messages that defined the purpose of the armed struggle. As a “man of freedom”, Teddy calls himself, intrinsically, Teddy Afro serves as a singer of freedom, unity and change. 

Teddy the aesthetic and philosophical singer

Tewodors Kassahun was born on 14 July 1976 in Kuas Meda area, Addis Abeba. Teddy Afro is one of the few singers whose poems and speeches are highly researched, well thought and measured. His motto, “Love Wins” has been adopted by our team De Birhan Media as our official motto. Abel’s book mentions some of the few sayings of this young singer.

Secondly, Teddy knows the aesthetics of music. He knows and does represent that music is a scientific discipline that requires a concerted research and study. Therefore, he reads, listens and writes music carefully. Music books state that music theory connects four fields of study, such as hearing, singing, reading and writing as shown in the diagram below.

Hearingreadingsingingwriting.jpg

Reading and hearing of music is introvert while singing and writing are extravert acts. Hearing and singing are mainly performed through the good ears of the musician/audience while reading and writing of music are done via the musicological eyes of the musician/listener. A good artist converts these acts into theories in the brain and makes them practical when it is finally produced as a musical output.  Teddy Afro exceptionally from other singers owns these musical interconnections. He listens to other’s music carefully, reads poems, lyrics and all forms of publication from history to current affairs, writes amazing poems that listen to the heartbeats of the audience and sings it beautifully as a result. Taking his latest Tikur Sew/Black person song/Album as an example is worthy here. This song sung as a tribute to Ethiopia’s unifier and sole black African king that defeated a white Western colonising nation, Italy has been labelled by some as “”Ethiopian History/ The Battle of Adewa 101” comparing its deeply researched, analysed and composed lyrics with Freshman Ethiopian history courses offered in Ethiopian universities. This shows the reading and writing aspects of music theory legibly inscribed in Teddy's new album. Similarly, the diatonic arrangement, multilingual singing and voice insertions in Tekur Sew explain the hearing and singing musical qualities and innovativeness of the singer.  
Aesthetics is a sub-discipline of philosophy. Musical aesthetics as a sub genre of it then studies music based on qualities including  lyricism, harmony, hypnotism, emotiveness, temporal dynamics, resonance, playfulness, and color. With a close watch, most of these characteristics of music are boldly observable in most of Teddy Afro’s songs.

Most listeners due argue that Teddy Afro's songs are of emotions and categorically criticize him.   Peter Kivy's analytic philosophy  inspired extensive debate about the nature of emotional expressiveness in music. Most theoretical definitions of music define music as an art of emotiveness.  The fact that Teddy sings emotive songs puts him at the top of musicologists than wannabe singers. Emotiveness has to be expressed in music; that is the role of music.  As to Stanford.edu, those who take the experience of music's expressiveness to be a more intimately emotional one (through being predicated on imaginative engagement with the music, say), tend to emphasize that experience as more central to musical understanding, and thus attribute a larger part of music's value to its expressivity. Expressivity is the core part of Teddy’s music in addition to emotiveness. In this day and age of inflation when citizens cannot even afford to buy chicken, millions of Ethiopians bought Tewodros’ album; understandably because his songs are emotive and expressive of their feelings and life.

The Free Dictionary online version dictionary defines lyricism as tthe practice of writing verse in song form rather than narrative form to embody the poet’s thoughts and emotions. A verse that would in short exemplify this definition from the track title “Sele Fiker” meaning for love from his new album is:
አፈር ይዞ ውስጡ አረንጓዴ፣

ለምን ይሆን የራበው ሆዴ፡፡
This can literally be translated as:
With a soil which is green inside
Why is my stomach starving?
This verse states that Ethiopia contains a fertile soil and land but the nation, millions continue to be hungry and self insufficient. The singer taking himself as the first person character emotionally questions the moral of himself and his compatriots for being stationary than changing the status quo social-economic scenario.  Such exuberance and many other types of lyricisms are exhibited in the singer’s lyrics which are all written by himself. Teddy also introduces new concepts, philosophers, ideas, and personalities. In this new album, he sings about a new character (on the Sele Fiker track) new to most of the Ethiopian music audience, named Tewanye.  Tewanye was a thinker and philosopher who lived around five hundred years ago in Gonder, Ethiopia during the reign of Atse Eyassu. Little has been mentioned or written about him. Teddy now pokes us to read about this philosopher and why we have not followed his steps and moved forward.

Some listeners categorically put Teddy as a bad musician/ unmelodious while many select tracks from his albums that are bad and argue that although he is a good musician, he also has or produces bad music (bad seen against the above aesthetics of music).  Simon Frith (2004) argues that, "'bad music' is a necessary concept for musical pleasure, for musical aesthetics."  Therefore, the fact that Teddy “has or produces bad music” doesn’t necessarily make him unworthy as they rather do beautify the musical aesthetics. Teddy was released from jail in August 2009 for good behaviour, after he served over two years in jail for an alleged hit and run which most consider was “politically concocted attempt of silencing the politically justice minded singer”. Tikur Sew came out after 7 years of his last album….with a reportedly over 5.7 million copies sale in two days. Sources say that Addis Fortune reported on its Saturday 14 April issue that around 300,000 tape and half a million CD distribution was made for the first phase, which makes a turn over sales of 15,000,000.
What makes Tekur Sew spectacular? And why should it be listened? 
1.      Record breaking album sell – Since the entrance of the legendary singer Teddy Afro into the Ethiopian musicospehre. His latest album has reportedly been sold for over 4.6 million birr. Within four days of the release more than six million copies of the song have been sold, according sources close to the artist.
2.      Putting King Menelik II on the map : the singer has put the imminent king of Ethiopia and the black world, called by many who love and respect him Emyee, though with lots of opponents that consider him as a “massacring colonialist”, has been ignored by the current regime as an “enemy and suppressor of their regional kings and regionalism”. Indeed, the negative paintings and falsifications of Menelik II's role was kick started by Western colonialists and supremacists who were humiliated by him. Various books have been written, some Ethiopian ethnic groups have been blindly indoctrinated about the “genocide” Menelik excuted on their ethnic groups. As if there was an expansionist, unifier, and  a nation formed through round table, many Westerner’s and their disciples accuse the Emperor of being brutal while unifying Ethiopia. One strategy applied was fomenting hatred between the two major ethnic groups of Oromo and Amara using Menelik, an Amara (although his mother was an Oromo) as a source of difference. Higher officials and members of the incumbent ruling party TPLF including the Prime Minister Meles Zenawi have spoken and written books that negatively criticized and despised Emperor Menelik II, his ethnic group and any form of association with him. As a result of which the legacy and fame of the Emperor and mentioning his name and roles has been low key. But thanks to the brilliant singer, Teddy has put Emperor Menelik II back on the map. This song beautifully serves as a history reference album. Most feature films and movies  in Ethiopia cost around half a million birr to produce. 
   This song of Teddy, Tekur Sew soon to be released alone cost over 400,000 birr. Many Westerners have also taken part in the shooting of the clip. Hundreds of Addis Abeba University students who took part in the shooting were paid around 500 birr per person. One student said in an interview before Easter "Thanks be to Teddy now that I have my 500, I have money to pay my transportation cost to visit my families of the holiday in rural Ethiopia."
3.      Unifier: Although there have been some reports that stated that Teddy had made factual errors in the naming and context of some incidents in his Tekur Sew lyrics, broadly speaking, it is a well written factual lyrical story that attempts to bring all ethnic groups and their roles in defending  Ethiopia’s sovereignty  to light. There has never been such a music “popular” not traditional, that has such a caliber, mixing and artfulness. Importantly, it has a message of unity. Menelik, the history of Ethiopia and ethnic issues may be very controversial and divisive topics but one thing that Teddy boldly asserted in Tekur Sew is that we all have one commonality that unifies and bonds us, Adewa. The battle and victory of Adewa equalise and justify why we should be together. In the political context, the current togetherness of Ethiopian opposition groups mainly led by formerly secessionist Oromo groups and centralist and unitarist parties receives an indirect endorsement from Teddy’s super production. This art of timely release, as expressed by musical gurus  fulfill the  musical values of emotiveness, timeliness and expressiveness. Additionally, he mixes Amharic and Oromigna languages in this album title, and says ‘ Ijoollee Biyya Keenyaa ’ in  ‘My Children of my country  with a simile that our similarities are greater than our differences.
4.      Aesthetic values: Tekur Sew contains the major aesthetic qualities such as including  lyricismharmonyhypnotismemotiveness, temporal dynamics, resonance, playfulness, and color. Most of the negative, corrective and promotional comments, reviews and criticisms are indications of the music aesthetic values. Tekur Sew, Sele Fiker and Afrikaye hinge the listener to wake up and dance while haile, helm ayedeegemem, Fiyoriana and setehed composed in a slow, low tone and rhythm force us to sit back relax and reflect.
5.      The title: Tekur Sew literally meaning Black Person/man is out of the customary grammatical naming norms and the vocabulay meanings of naming album titiles. Many wondered what he meant by Tekur Sew when the album was promoted months before its release. Blackness or being black has been little used in literary and music arts worldwide or in Ethiopia. Frantz Fanon is one of the few to popularize blackness and color related post colonial theories and broach the issue of colour into the academic discourse. Teddy Afro now ascribes the phrase Black Person/man an honorable and eminent status and class by artistically deconstructing it through King Menelik, pride of black people. This academic song needs to be translated and studied by Afrocentrist thinkers and academics. 
6.      Helping the altruist artist: Teddy Afro’s popularity hiked mainly due to his humanitarian and altruist activities.  According to Abel Zebene’s book Teddy Afro’s humanitarian activities began when he started visiting Abebech Gobena Orphanage in Addis Abeba and began donating money. He has been successively supporting the orphanage. Abel writes that the founder of the Orphanage had once asked Teddy Afro to take over the Orphanage and administer it himself. Some of his altruistic and humanitarian activities among many include: donation to those affected by floods in Dire Dawa, financially assisting the late artist Manalemosh Dibo when she was ailing in hospital, giving around one million birr of the income from his concert in Addis Abeba Stadium to a local NGO that worked with street children and beggars and the recent ransom payment of over 700,000 birr for the freeing of an Ethiopian young man arrested in Somaliland. In addition to these, he called for a u-turn of thoughts; this young philosopher taught many to be generous, lovers, optimist, mannered, humble, nationalists, and unified by being an example. The Teddy Afro phenomenon is a phenomenon that has removed the Dergistan and TPLFized old phenomenon of jealousy, hate, contempt, selfishness, bitterness and despotism and replaced them with all those that negate these.
Similarly, around 10 of his songs are composed by an upcoming novice music composer named Michael Hailu. By this, Teddy is assisting Michael financially, networks and  making him popular.
Critique
1.      Libe/leben: The most over used word in the new album of Teddy Afro is Lebe/my heart. This writer came across a good number of times in almost all his lyrics. Such repetition should have been removed.
2.      Exclusion of a verse: In the song titled “Hayle” or power, Teddy inserts a poem from the legendary Ethiopian Laureate Tsegaye Gebremedhin’s poem titled Feran (we are afraid). For deliberate or unknown reason Teddy excludes a line from the poem that reads “የነፍስን አንደበት ዘጋን” meaning we have closed/censored the voices of souls. The singer might have chosen to quote the last few verses of the poem but still makes it an incomplete poem and de-copyrights Tsegaye. 
3.      Monotonity of love theme and beats: Repetitive themes of love are heard in most of his songs. Like many other singers, they were dominated with monotonous themes of love of a girl. The music composition also shows similarity from one another, this may be due to that fact that around 10 of the songs were composed by one music composer. Resembling beats are heard in most of them.

Conclusion
Some years ago when I was a novice of the Weston world, I was the usual Ethiopian young man curious to know the psyche, behavior of the western man and their views re: Ethiopia. I happened to make few good friends. One of these good friends has been an older man of good breed and with high infatuation of Ethiopians and Ethiopia. This man one day gave us folded gifts to use it as we had nothing to do then and were all “an illegal aliens”. As soon as I arrived home, I opened the gift. It was Teddy Afro’s Yasteseryal album. This is the extent that Teddy Afro has colonized the minds of Western audience. Many people that I find in this part of the world know only two things about Ethiopia; famine and HIM Hailsesllasie. But now there is a third addition; Teddy Afro, Ethiopia’s new brand name.  Tikur Sew is a success; if art is to be a scientific and philosophical tool of peace, development and reconciliation, there is no better examplar.
Teddy afro is an inspiration of the new generation. African youth can be inspired by their artists and exemplary icons when their barrel holding leaders fail them. Tewodros is one of those that inspired Ethiopians all across the world to think twice about the value of their unity, love and freedom. Teddy Afro has made his fiancée public; winner the title of Miss Ethiopia 2006 and an independent journalist and film director by profession. We wish them well.
The poem below summates my point of view in this write up. It is a poem put as comment under Dawit Kebede's article. Tekur Sew is a pill to those diseased with hate and falsehood


አቢይ ኢትዮጵያዊ ሥጋዊ ወመንፈሳዊ 
April 17, 2012 at 8:48 am
*******ጥቁር ሰው እንደዶሮ::*******
የፋሲካ በዓል ቢመጣ ዘንድሮ:-
በቴዲ ታረደ
ጥቁር ሰው እንደዶሮ::
አወይ መሞት ኖሮ:-
አይበስልም ወይ አሮ???
እርር ብሎ ከስሎ:-
የበሰለ መስሎ:-
በሕዝብ ደም ተማስሎ:-
ባጥንት ተቀቅሎ:-
በምንሊክ ምጣድ ቢራገብ ዘንድሮ{-
በካሴት ታረደ
ጥቁር ሰው እንደዶሮ::
ለነጻነት ችቦ በኤሎሄ ትንሳኤ:-
ለኢትዮጵያ ተስፋ ለሕዝቧ ሱባኤ
በሙዚቃ ቅላጼው ታሪክ ሊያመላክት:-
በእስር በወከባ በፍቅር ሲዋትት:-
አመታት ሲያስቆጥር ፋሲካን ዘንድሮ:-
ቴዲ አረደልን
ጥቁር ሰው እንደዶሮ::
እንግዲህ ትንሳኤ ነጻነት የሚሻ:-
ትግል ጎራ ይግባ ይቃመስ ከጉርሻ::
አውቆ የተኛ ሰው ፍፁም አይነሳ:-
ሕሊናውን አልፎ ልቡ እስከሚበሳ::
እናም በፋሲካ መግደፊያው ዘንድሮ:-
በቴዲ ታረደ
ጥቁር ሰው እንደዶሮ::

Let’s promise to put Emye Menelik back on the map!
Viva Emperor Emeye Menelik, pride of the black race and God bless the young thinker, Teddy Afro!!!!!!!!


By T, Staffer of De Birhan Media
17 April 2012