Friday, May 4, 2012

በውቀቱ ስዩም

www.facebook.com/tarikuasefaክልክል ነው

ማጨስ ክልክል ነው
ማፍዋጨት ክልክል ነው
መሽናት ክልክል ነው
ግድግዳው በሙሉ ተሰርቶ በክልክል
የቱ ነው ትክክል?
ትንሽ ግድግዳና ትንሽ ኃይል ባደለኝ
"መከልከል ክልክል ነው"፤ የሚል ትዕዛዝ አለኝ፡፡


(በእውቀቱ ስዩም፣ የ፣ሣት ዳር ሐሳቦች፣ 2000)
 ደመወዙን ቢጥል
አንስተው ጠጡበት
ባርኔጣውን ቢጥል
ወስደው ደመቁበት
ከዘራውን ቢጥል
ተመረኮዙበት
በሄደበት ሁሉ
እየተከተሉ
በጣለው ሲያጌጡ
በጣለው ሲያተርፉ
ራሱን ሲጥል ግን
አይተውት አለፉ

በውቀቱ ስዩም
(ካንድምታ ላይ የተወሰደ )
 መሆን አለመሆን

በመሆን እና ባለመሆን
በማድረግ እና ባለማድረግ
በሁለት ታዛዦች ስር መውደቅ ነው
ሰው የመሆን ትልቅ ህግ
ሊኖሩት በማይፈቅዱት ህግ
ሊፈጽሙት በማይሹት ስህተት
በጣምራ ግጭቶች መሃል መቆም ነው ሰው የመሆን ሰውነት
ይሄ ሁሉ ፍጡር ይሄ ሁሉ ፍጡር
በፍጥረት መድረክ ላይ የሚርመሰመሰው
ላንዲት ቅጽበት እንካን ሰው ሆኖ አያውቅም ሰው ሊሆን ጽንስ ነው
ሰው እስኪሆን ድረስ አንዳንድዜ አምላክ አንዳንዴ ሰይጣን ነው።
ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
መሸ ደግሞ አምባ ልውጣ!

አምባ ወጥቼ እኩለ-ሌት ፤ ስለት ገብቼ በስሟ
ከርሞ ሰይጣን በሷ አስቶኝ፤ ልገላገል ከህመሟ
ጠበሏ አፋፍ በጨረቃ፤ ደጋግሜ፤ ማህሌት ቆሜ
ሆዴ ቃትቶ ባር ባር ብሎ፤እርቃኔን ከሷ ታድሜ
ደጀ ሰላሟን በአራት እግር፤ ተንበርክኬ ተሳልሜ
በስጋዬ እሚነደውን፤ በጸሎት ላቤ አጣጥሜ
እፎይ ብዬ አመስግኜ፤ ውዳሴዋን ደጋግሜ...
ገና ከደጅዋ እልፍ ሳልል፤ ደሞ ይምጣ የቁም ህልሜ?
ሌት በጥምቀቷ የነጣው፤ ነጋ፤ ደፈረሰ ደሜ።
ለሷ እንጂ ለኔ አልያዘልኝ፤ አዬ የስለት አታምጣ!
በውጣ ውረድ በጠበል፤ ባሣር ወዜ ቢገረጣ
ልክፍቷ እንደሁ አልለቀቀኝ፤ መሸ ደሞ አምባ ልውጣ!

ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድሀን፣ እሳት ወይ አበባ

No comments:

Post a Comment