Thursday, May 3, 2012

ይድረስ ለእናት አለም


ይድረስ ለእናት አለም፡-www.facebook.com/tarikuasefa

በጣም ለምወድሽ እናቴ እናት አለም ! እንደምን ሰንብተሻል

አባበዬስ እንዴት ነው? እኛ ከወንድም ጋሼ ፀባይ መለዋወጥ

በስተቀር ደህና ነን፡፡ እናት ዓለም ብቻ አንድ ወንድ ልጅሽን ያቺ

ቀልቃላ ገርል ፍሬንዱ ምን እንዳስነካችው ባይታወቅም አብሮን

እንዳልተወለደ አሁንማ ስልኩንም ለማንሳት ኮርቷል፡፡

በየሳምንቱ እሷን ይዞ በየሀገሩ መብረር አምጥቷል፡፡

እናት አለም! እናንተ ለፍታችሁ አንዴ ፈረንሳይ ት/ቤት፤

አንዴ ፈረንጅ ሀገር ብር እየመነዘራቸሁ አስተምራቸሁ ዛሬ

ይቺ ከይሲ በአናት መጥታ የተዘጋጀ እና ያማረ ቤት ልትገባ

ዳር ዳር ትላለች፡፡ በዛ ላይ ደግሞ እሱ እሷን ተዋወኩ ብሎ

አዲሰ ማርቼድስ አውጥቶ የድሮውን ቢ..ኤም..ደብሊው ለእኔ

ይሰጠኛል ስል እሷው በቀደም ይዛው ስትደናብር መሀል ከተማ

Aየኋት፡፡ በዛ ላይ አለባበሷን ብታይ እኮ ጭንቅላትሽን ይዘሽ

ትጮሂያለሽ፡፡ የተወለደ ሀጻን ጭንቅላት የሚያካክሉትን

ጡቶቿን እያሳየች ነው የምትሄደው፡፡ ትንሽ እንኳን እፍረት

የሌላት ጉድ በየድግሱ ቤት ወንበር እያለ እሱ ላይ ነው

የምትቀመጠው፡፡ ሌላው ደግሞ እንደ በሽተኛ እሱ ነው

የሚያጎርሳት ብትሞት በእጇ አትበላም፡፡ እኔማ ገና ሳያት ነው

ደሜ የሚፈላው፡፡

ብቻ ልጅሽን ምን እንዳስነካችው እራስሽ መጥተሽ

ብትጠይቂው ይሻላል፡፡ በዚያን ሰሞን ቹቹ የመኪናዋ ቁልፍ

ጠፍቶ ስራ ውሰዳት ብዬ ብደውልለት ታከሲ ይዛ ትሂድ ስብሰባ

አለበኝ አለኝ፡፡ ለድሮው የእኛ ነገር የማይሆንለት ይኸው እሷን

ካገኘ ወንድምነቱን ሁሉ ረስቶታል፡፡ ከሁሉ ከሁሉ የምፈራው

አውቃ አርግዛበት ጠቅልላ ለመግባት ሠርጌን ደግስ እንዳትለው

ነው፡፡

እንደው አናት አለም እሷን ካገኘ ፀባዩ ሁሉ ተቀያይሯል፡፡

ባለፈውማ ይባስ ብሎ ለልደቱ የገዛሁለትን የሱን ቱታ ለብሳ

ስፖርት ስትሰራ ስፖርት ቤት አገኘኋት፡፡ ደግሞ አማረብኝ ብላ

ያንን እሱው ያሰራላትን ነጭ ጥርሶቿን ታሳየኛለች፡፡

እንደማትወደኝ እኮ ያስታውቅባታል!! ከሁሉ ከሁሉ ቹቹ ታክሲ

ይዛ ትሂድ ያለውን አልረሳውም፡፡ እናት አለም መቼም ጉድሽን

የሚነገርሽ የለም ብዬ ነው የምጽፍልሽና ነገ ጠዋት አንቺንም

በዚች በቀዥቃዣ ሳይለውጥሽ አንድ ነገር አድርጊ፤ ምንም

ቢሆን እኛ ሥጋዎቹ ነን፤ ከአንድ ሆድ የወጣነውና አንድ ጡት

ጥበተን ያደግነው እኛ ነን፡፡ እሷ ባዳ ናትና አንድ ነገር አድርጊ፡፡



                                                      ልጅሽ ሳሮን

የእናት አለም የመልስ ደብዳቤ

ለምወድሽ ልጄ ሳሮንዬ ለመሆኑ የላከሺልኝን ደብዳቤ ሰትጽፊልኝ ምን

ዓይነቱ ስይጣን ነው ሰፍሮበሽ የነበረው! እንዲህ ዓይነት ልጅ ነው

የወለድኩት አሰኘኝ፡፡ እግዚአብሔር የቀንና የማታ ጸሎቴን ሰምቶ ለአንድ

ወንድ ልጄ ውሃ አጣጭ የትዳር ጓደኛ ቢሰጠው የአንቺ እንቅልፍ ማጣት

ምን ይባላል?

የእኔ ልጅ! እንዳልሽው ከአንድ ሆድ የወጣችሁ አንድ ጡት ጠብታችሁ

ያደጋችሁ ወንድምሽ ነው፡፡ ወንድም እህቱን እንዲያገባ ሃይማኖታችንም

ባህላችንም አይፈቅድም፡፡ ወንድምሽን አንቺ አታገቢው፤ ምን አድርጊ ነው

የምትያት? የእኔ ልጅ ይኼው እሷን ካገኘ ጊዜ ጀምሮ የላከልኝ ፎቶ

ይኸው መልኩም መለስ ብሏል፡፡ በሳምንት በሳምንትም ይደውልልኛል፡፡

እሷንም በስልክ ደውሎ አስተዋውቀኝ፡፡ አደራ ብያትም ይኼው የሆቴል

ምግብ ከበላ ሰንበቷል፡፡ የልጄን ደስታ በድምፁ አውቀዋለሁ፡፡ ይኼው

እናንተ ስትለመኑ ሰው እየፈለግን ነው ያላችሁትን መድኀኒት እንኳን

እሷም አይደለች እንዴ የፊት ቅባት ሳይቀር ጨምራ በፖስታ ቤት

የላከችልኝ፡፡ ሌላው ደግሞ ነርስ ነች አለኝ፡፡ ልጄ ቢያመው እንኳን አጠገቡ

አለችለት፡፡

አንዳታረግዝ ነው የምፈራው አልሺኝ? በየቤተክርስቲያኑ የምሳለው ስለቴ

ደርሶልኝ የሱን ፍሬ ሳልሞት ባይ ምናለበት፡፡ አንድ ሳይሆን መንታ መንታውን

ባረገዘችልኝ፡፡ አንቺ የሰው ኑሮ ውስጥ ገብተሸ ከምትበጠብጪ ሰው መናቁን

ትተሸ ብታገቢ ለወሬም ጊዜ አየኖርሽም ነበር፡፡

የእኔ ልጅ! ጡቷን ማሳየት ቀርቶ ራቁቷን ብተሄድ ፖሊስ ካልያዛትና ልጄ

ከወደዳት አንቺ ምን ጥልቅ አደረገሽ? ቢወዳትም አይደል እንዴ እዚህ ድረስ

ደውሎ ያስተዋወቀኝ፡፡ የኔ ልጅ መፅሀፉም የሰው ልጅ እናት እባቱን ይተዋል፤

ከሚሰቱ ወይ ከባሉ ጋር እንድ ይሆናል ነው እንጂ የሚለው ወንድም እህቱን

ያገባል አይልምና ወደ መንፈስሽ ተመልሰሽ አምላክሽን ይቅርታ ጠይቂ፡፡

የወንድምነቱን ከሚገባው በላይ አድርጓል ወይስ እድሜ ዘላለሙን እናንተን

ሲያስተምርና መኪና ሲገዛ እንዲኖር ነው ምኞትሽ፡፡

ልጄ! ልብ ብለሽ አያትሽ የነገረኝን ይሄንን አፈ ታሪክ አንበቢ፡፡

“ሚስት ከባልዋ ተጣልታ ዛሬውኑ መጥታችሁ ካላፋታቸሁኝ ራሴን

እገላለሁ ብላ አናት አባቷ ጋ መልእከተኛ ትልካለች፡፡ እናትና አባትም

ደንግጠው ሊያፋቱ ሲከንፉ በሌሊት ልጃቸው ቤት ይሄዳሉ፡፡ ድንገት በሩን

ከፍተው ሲገቡ ልጃቸው ከአልጋዋ ዘላ ወርዳ ራቁቷን ትቆማለች፡፡

ድንገትም በር የከፈቱት እናትና አባቷ መሆኑን ስታይ አፍራ ቶሎ ብላ

ፊቷን ወደ ባሏ ጀርባዋን ደግሞ ወደ እናትና አባቷ አዞረች፡፡ ምንም

እንኳን ልትፈታው የተዘጋጀችው ባሏ ቢሆንም ባሏን ሳታፍር እናትና

አባቷን አፈረች፡፡”

ልጄ ሳሮን የእናትና የአባት ፍቅር ዘላለማዊ ቢሆንም የወላጅንም ውለታ

መመለስ ተገቢ ቢሆንም ከባልና ከሚስት የቀረበ የለም፡፡ ስለዚህም ነው

ባልና ሚስት አንድ አካል አንድ አምሳል ናቸው የሚባለውና ቦታሽን

Aውቀሽ የሰውን ሕይወት አትበጥብጪ፡፡ አፍ አለኝ ብለሽም እንዲህ

አይነት አሉባልታ ሁለተኛ እንዳትጽፊልኝ፡፡ አንቺ አግብተሸ ብትወልጂ

ወንድምሽ ደስ እንደሚለው ሁሉ ለእሱም አንቺ ደስ የበልሽ፡፡

እግዚአብሔር ጥሩ ልቦና እንዲሰጥሽ እጸልይልሻለሁ፡፡

እናትሽ እናት እለም

No comments:

Post a Comment